Monday, November 4, 2013

ከዓይን ላይ የሚነሣ መንፈስ (ቡዳ)



ከዓይን ላይ የሚነሣ መንፈስ (ቡዳ) ሰዎችን የተለማመደ ለዘናት ከሰው ልጆች ጠባይ ጋር ተመሳስሎ የኖረና ዘሩ ያደረገ ዓይነቱ ይለያይ እንጂ ሰውን በከፍተኛ ደረጆ የማጥቃት ልምድ ያካባተ የቱጋ ይዞ መቼ እንደሚጥል መረጀ ያለው ከመተቶች ሁሉ በበለጠ ሁኔታ የከፋ ጉዳት የሚያደርስ ከአንድ ወደ ሌላው ረቀቅ ባለ ችሎታ የሚተላለፍ አደገኛ የሆነ መንፈስ ነው : : ከዓይን ላይ የሚነሣ መንፈስን በአጭሩ (ቡዳ) በማለት ይጠራል : :

( የመንፈሱ የመግቢያ አቅጣጫዎች )

- ከቤተሰብ የሚወረስ ዛር ብዙ ጊዜ የቡዳ መንፈስ መነሻው ከእናት : ከአባት : ከአያት :
ከቅድመ አያት : ከቅም አያት ወዘተ . . . ሲወርድ ሲዋረድ የመጣ ዛር ሲሆን በመዋለድ በአካል በደምና በነፍስ ውስጥ ተዋሕዶ እየተወራረሰ እንደ ልክፍት የሚይዝ ነው : :

- በሌሎች ላይ የሚያርፍ መንፈስ ይህ ከመነሻው ተሸጋጋሪ ሳይሆን ከውጪ ወደ ውስጥ በዓይን አማካኝነት ወደ ሌሎች የሚሄድና በሌሎች ላይ የሚያርፍ መንፈስ ሲሆን በሇላም ተመልሶ ከውሰጥ ወደ ውጭ ሌላውን ለመብላት የሚንቀሳቀስ ጠላት ነው : : ከሰባት ዓመት በሇላ ግን ራሱ ቡዳው ተሻጋሪ መንፈስ ይሆናል : : መንፈሱ በሰውነትችን ውስጥ ሥፍራ የሚዘው በሶስት ባታዎች ላይ ነው : :

1. በደም ውስጥ

2. ሥጋ ላይ

3. ነፍስ ጋር

* በደም ውስጥ የሚቀመጥ የቡዳ መንፈስ በደም ውስጥ የተዋሐደው ይህ መንፈስ አንዳንድ የደም ግብሮችን የለመደና የሚጠይቅ ዶሮ : በግ ወዘተ . . . እረዱልኝ
የሚል አልፎ ተርፎም አምባ ጐር አስነስቶ በዚሁ ጸብ ሣብይም ደም ማፍሳስ ደም ሲፈስ ማየት የሚፈልግ መንፈስ ነው : : በዝህም ምክንያት የቡዳውና መንፈስ ተለውጦ
የዛሩን ጠባይ ይወርሣል ማለት ነው : :

* ሥጋ ላይ ያለ የቡዳ መንፈስ ዓይን ላይ ተቀምጦና ከዐዓን ላይ እየተነሣ ሌሎችን
ለማጥቃት የሚሰማራ መንፈስ ነው : :

* ከነፍስ ጋር የተዋሃደ የቡዳ መንፈስ በዚሀ ሄደት ክፉው መንፈስ መቶ በማቶ ከነፍሳችን ጋር ተዋሕዷል ማለት ነው : :

ይህንን ከውሰጣችን ለመለየት ብዙ ጊዜ ያየሚፈጅ ሲሆን ተከታታይ " የቅድስ ቁርባንና" የጸሎት ሥርዐት ያስፈልጋል : : ምክንያቱም ነፍሳችንና መንፈሱ አንድ
በመሆናቸው ነው : : ይህ ከነፍስ ጋር የተዋሃደ መንፈስ ሥር የሰደደ መሰረት ስለያዘ ጥቃቱ ከበድ የለ ነው : :

በዚህ ዘመን ከነፍስ ጋር በፍጥነት ለሚዋሃዲ መንፈሶች ምሳሎ የሚሆኑን የመናፍቅና የዶ/ር ራምፓና የኦሾ የሣይኮሎጂ መንፈሶች
ናቸው : :

{ የመንፈሱ የጥቃት መንገዶች }

- የራሱን የሰውየውን ነሮ የሚበላ መንፈስ
ገንዘቡን ጊዜውን በአጠቃላይ በረከቱን ሁሉ እየበላ ዕድሜ ልኩን እንደባዘነ እንደደከመና እንደባከነ እንዲኖር ያደርገዋል : :

- ዕድልን የሚበላ መንፈስ ሁልጊዜ ከጠማማ ከክፉ ከሙዋርተኛና ጠባዩን ከሚያበለሽ ሰው
ጋር የሚያገናኝ መንፈስ ነው : :

በአጠቃላይ ዕድሉ ከመጥፎ ሰው ጋር ስለሚያውለው የራሱ ጠባይ ወደ ክፉት ያዘነበለ ይሆናል : :

- እየበላ የሌሎችን ሕይወት የሚያበላሽ የቡዳ መንፈስ ከላይ የተጠቀሱት ሁለቱ የቡዳ የጥቃት መንገዶች ከአካላዊ ጤና ጋር በቀጥታ የተገናኘ ጉዳት የማያደርሱ ሲሆኑ ይህ ሶስተኛው መንፈስ ግን አካልን የሚይዝ የሚበላ ጤናን የሚያውክና አዚም የሚሆን መንፈስ ነው : :