Wednesday, June 24, 2015

ተናገሩ ድንቅ ስራዉንም መስክሩ

"ተናገሩ ድንቅ ስራዉንም መስክሩ"
ከአዲስ አበባ 650 ኪሎ ሜትር መጓዝ ግድ ይላል ታላላቅ የገጠር ከተሞች አሉ በተለይ ከጊቤ በረሃ እንደተሻገርን ግራና ቀኝ አይናችንን እንዲንከራተት ፈቀድንለት ወሊሶ፣ ወልቂጤ፣ ጅማ፣ በደሌ፣መቱን እንዳለፍናት ጎሬ ስንደርስ አንድ ሐውልት ከቤተክርስቲያኑ በር አካባቢ በግርማ ሞገስ ተሸፍኖ ቆሟል፡፡




"ብጹዕ አቡነ ሚካኤል"
ይባላሉ ፋሽስት ኢትዮጵያን በወረራት ጊዜ ልክ እንደ አቡነ ጴጥሮስ በተመሳሳይ ጊዜ ህዝቤም መሬቱም አይገዛልህ ብለው በማውገዛቸው በግፍ በመትረየስ ተረሽነዋል ተገድለዋል፡፡ሰኔ23
ከፓትሪያርኩ ጀምሮ ብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በተገኙበት የሐውልት
ምርቃትና የሰማዕትነትን ስም ያገኛሉ፡፡
ይህንን በረከት ለመሳተፍ ከመላው ኢትዮጵያ በርካታ ህዝብ ከየአካባቢው ይጎርፋል፡
እኛም ተገኝተን ሰፊውን ታሪክ ያኔ እናቀርባለን፡፡
የኢሉባቡር ሀገረ ስብከት ይህንን ታላቅ በዓል
ሐይማኖቱንና ታሪኩን የሚወድ ኢትዮጵያዊ ሁሉ
እንዲገኝ ጥሪ አቅርበዋል፤ይኸው ይድረሳችሁ፡፡

በተለይ ጅማን ይዛችሁ የኢሉባቡር ክልል በግራና
በቀኝዎት ጥቅጥቅ ያለው ደን የተለያዩ የዕጽዋት
ዘር ያለበት ሲሆን በተለይ አመቱን መሉ በአረንጓዴ የተሸፈነው እጅግ ውብና ማራኪ ስፍራ፦ ቀረሮ፣ሰሳ፣ዋንዛ፣ማንጎ፣አቡካዶ፣ቡና፣በቆሎ የመሳሰሉት ተክሎች ይገኙበታል፤
አንዳንዴም እንደው የራበው
መንገደኛ ጫካ ውስጥ ገባ ብሎ ቢወጣ የእለት ጉርሱን አያጣም ይባላል፡፡
አሁን ትንሽ ጉዞ ነው የቀረን ጉመሮ ሻይ ቅጠል ሰፊ የእርሻ መሬት ላይ ደርሰናል
"የመስሊሟ ታሪክ ጀመረ"
፦የዛሬ 3ወር እዚህ ቦታ ላይ
14ሰው የተፈቀደለት ዶልፊን መኪና የዛን ዕለት ግን
27ሰው ጠቅጥቆ ከመቱ ወደ ኡካ ከተማ ጉዞ ጀመረ ፀሐይ ለጨረቃ ፈረቃዋን ቀይራለች ጭለማው በርትቷል የመኪናው ከፍተኛ ፍጥነት ቀጥሏል ከምሽቱ 1ሰዓት ግን ፊለፊቱ ቢራ የጫነ የጭነት መኪና ጋር ፊት ለፊት ተገናኙ ያኔ ነበር እጅግ የአመቱ ዘግናኝ አደጋ ነው የተከሰተው 11ሰዎች ወድያው ላይመለሱ አንቀላፉ ፤ከባድ ጉዳት የደረሰባቸውም አካላቸውን አተዋል ታዲያ "አዋጉ ሠኢድ ኢመማ"
አምቡላንስ እስኪመጣ ከ11አስክሬን ጋር ቅጠል
አልብሰዋት ከሞቱት ጋር ተቆጠረች፤በቆይታ በኋላ
ፊቷ በደም ቢሸፈንም የተረፈው አንድ አይኗ እንደመንቀሳቀስ ሲል የአምፑላንሱ ሹፌር ድንገት
አይቷት ከሞቱት መካከል ለያት ወደ መቱ ሆስፒታል
ሄደች አልተቻለም በኮንትራት መኪና አዲስ አበባ
ጥቁር አምበሳ ሆስፒታል ታከመች፤ እንደ እድል ሆኖ
የተሰበረው እግሯን ሳይጠግኑላት በሚያሳዝን ሁኔታ
ወደ መንደሯ ተመለሰች፡፡
3ወር ሙሉ አትናገርም አትጋገርም ተኝታ ብቻ ማቃሰት መወራጨት ብቻ በሙስሊሞች ባህል ሁሉን አረጉላት መፍትሔ የለም፡፡
አንድ ነገር ቤተሰብ ተማከሩ ይሄ ነገር አንደበቷን የቆለፋት ሰይጣን ሳይሆን አይቀርም ብለው ወደ ቤተክርስቲያን አመሩ አባቶችንም አናግረው ወደ
ቤታቸው ጸሎት እንዲደረግላቸው ተማጸኑ
የቅዱስ ገብርኤልን ጸበል ቤተሰቦቿ በጀሪካን ይዘው
ቀሲስ ትህትና ደግሞ ዳዊታቸውን ሸክፈው አመሩ፡፡
እንግዲህ ሂዱና አህዛብን ሁሉ "በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃቹኃቸው" ያዘዝኳችሁን ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራቹኃቸው ደቀ መዛሙርት አድርጓቸው፡፡
እነሆ እኔ እስከ ዓለም ፍፃሜ ድረስ ሁል ጊዜ ከእናንተ ጋር ነኝ፡(ማቴ 28፥28)
እንደ ስርዓተ ቤተክርስቲያን ከዳዊት፣ውዳሴ ማርያም፣ ኪዳንና ትምህርተ ኀቡአት ካዳረሱ በኋላ
ጸበል እረጯት ጆሮዋም እየተከፈተ መጣ ለካ ከመኪናው በወደቀችበት ሰዓት አጅሬ ሰይጣን አግኝቷታል፡፡
ቀሲስ በሥላሴ ስም በድንግል ማርያም
ልጅ በኢየሱስ ክርስቶስ ስም እያሉ በመስቀል ይዳብሷታል ኡኡኡ እለቃለሁ አጋንንት ነኝ ጂኒ ነኝ መስቀሉ አቃጠለኝ,,,,,,ቄሱም እግዚአብሔርን አመሰገኑት ቤተሰብ "አንደበቷ መከፈቱ "ለነሱ እንደ ተአምር ነው በልባቸው ለገብርኤል ተስለዋል::
አሁን ልቀቅ አታሰቃያት ይሉታል ለቅቄ ወዴት እሄዳለሁ? በተረፈው አንድ ዓይኗ ወደ ቄሱ እያፈጠጠ
እያጓራ አንተላይ ወጥቼ ልምጣ እያለ መፎከር ጀመረ መሪጌታ ቀሲስ ትህትና፡ የእሷን ሰላም ማግኘት
እንጂ የአጋንንቱ ዛቻ አላስፈራቸዉም፤ግድ የለም
በእግዚአብሔር ቃል አሸንፍካለው ና!እያሉ ያናዝዙታል
ዳዊታቸውን ትራስጌዋ ላይ አድርገውላት 4ሰዓት ተኩል ላይ አረፍ ትበል ብለው ወደ ባለቤታቸው
ሱቅ ሄዱ፡፡
ከሱቃቸው ጎን ካለው ሻይ ቤት አረፍ እንዳሉ ኬት
መጣ ሳይባል ትልቅ እባብ ይጠመጠምባቸዋል
እስቲ ለአንድ አፍታ እግራችሁን አስቡት ለዛውም መርዘኛ እባብ ግማሽ አካሉ መሬት ሆኖ የተጠመጠመው አንገቱ ጉልበታቸው ላይ ደርሷል፡፡
" እንደ እግዚአብሔር ሐሳብ ለተጠሩት ነገር ሁሉ ለበጎ እንደሚል" ያ ልጅቷ ላይ ሆኖ የፎከረዉ አጋንንት ለካ ተከትሏቸዋል፡፡
"እነሆ እባብና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኃለሁ የሚጎዳችሁም ምንም የለም" (ሉቃ 10፥19)
እንዲህ ስገልጽላቹ ቀላል ይመስላል ቀሲስ እንደ ሰዉ ደካማ ናቸውና እየዘለሉ ለማስለቀቅ ብዙ ታግለው ከሳቸው ለቆ ወደ ሚስታቸው ሱቅ እንደተላከ ህፃን የተሳበ ሲገባ አንድ የሻይ ቤቱ ባለቤት ሙስሊም በዱላ ጨፍጭፎ ገደለው፡፡
ወድያው ለሙስሊሞቹ ተነገራቸው በስልክ
(ማሽ አላህ ማሽ አላህ) ተመስገን ለፈጣሪ ምስጋና ይገባው እያሉ የቄሱን እምነት አደነቁ
እኔም ይህ ተአምር ከተከሰተ ከ3ቀን በኋላ ለቅድስት ድንግል ማርያም ልደት በዓል እዛ ከተማ ተገኝቼ ስለነበር ሁሉንም ታሪክ ከሙስሊሞቹ ሰምቻለሁ፡፡
አንደበቷ የተከፈተውንም አውርቻታለው የምታዩትን ፎቶ አነሽቻታለው በመስቀል በቅባ ቅዱስ ቀሲስ እየጸለዩላት፡፡
ባለፈው የፉጡማ ጂብሪል አዲስ የኦርቶዶክስ እንግዳ ብያቹ ነበር፤ ልክ ነኝ
፨አሚራ የምትባለው ከSISI ነፍሰ በላዎችን መርጣ ወደ ሞት መንገድ ሄደች(ተቀላቀለች)ልብ ይስጥልን፤
፨ፋጡማ ጂብሪል ደግሞ በጥምቀት ወደ ዘላለም ህይወት ሰላምን መርጣ የሥላሴ ልጅነት አገኘች ህይወት የሆነውን የኢየሱስ የክርስቶስን አማናዊ ቅዱስ ስጋውንና አማናዊ ክቡር ደሙን ተቀበለች ዛሬ ማንም የማይቀማትን በጎ እድልን መርጣለችና ለእግዚአብሔር ምርጥ ዕቃ ሆነች፡፡በፎቶ ላይ እንዳያችሁት በሰንበት ትምህርት ቤት መዘመር ጀምራለች፡፡ ሁለቱ ወንድምና እህቶችም ከፉጡማ
ቀደም ብለው ወደ ክርስትናው ገብተዋል፦እንድሪስ መሐመድና አይሻ መሐመድ ናቸው፡፡ እግዚአብሔር ይመስገን ቀጣይ አንግዶቼ ይሆናሉ፡፡
የፋጡማ አዲስ ስሞ" ናርዶስ ጂብሪል"
"ስመ ክርስትናዋ ወለተ ሰማዕት"
ምስጋና ፦በአገልግሎት አብረውኝ የነበሩ ቀሲስ ታምራት
መ/ር ኤርምያስ አሰፉ፡ መ/ር መላኩ፣ለሰበካ ጉባኤ
ለሰንበት ትምህር ቤተ መዘምራን ለማህበረ ቅዱሳን፣
ለግርማና ለኡካ ነዋሪዎች ይሁን፡፡አሜን!!!
share በማድረግ ሐይማኖቶን ይመስክሩ፡፡
ለማንኛውም መረጃ ወይም አስተያየት በ Viber- what'sup ቁጥር 0911652083 መልእክት ማስቀመጥ ይችላሉ፡፡ቸር እንሰንብት,,,,

Wednesday, June 10, 2015

የወሊሶ ቤተ ሳይዳ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም

በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ምእመናን የተፈወሱባት የወሊሶ ቤተ ሳይዳ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ቅዳሴ ቤት ይከበራል አትም ኢሜይል
ግንቦት 8 ቀን 2007 ዓ.ም.
በእንዳለ ደምስስ
01w
በደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት በወሊሶ ከተማ የምትገኘው የቤተ ሳይዳ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም ሕንፃ ግንባታ ተጠናቅቆ ቅዳሴ ቤቱ ግንቦት 20 እና 21 ቀን 2007 ዓ.ም. ቅዱስ ፓትርያርኩ፤ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያንና ምእመናን በተገኙበት በድምቀት እንደሚከበር የገዳሙ አስተዳደር ገለጸ፡፡
የወሊሶ ቤተ ሳይዳ ደብረ ምጥማቅ ቅድስት ማርያም ገዳም በ1971 ዓ.ም. በብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ የተመሠረተች ሲሆን፤ በ1996 ዓ.ም. በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ የመሠረት ድንጋይ ተቀምጦ የሕንፃ አሰሪ ኮሚቴ በማዋቀር ግንባታው ቢጀመርም በተለያዩ ምክንያቶች ግንባታው ዘግይቶ በዐሥር ዓመቱ ሊጠናቀቅ እንደቻለ አስተዳሩና የሕንፃ አሰሪ ኮሚቴው ገልጸዋል፡፡

የቤተ ክርስቲያኑን ዲዛይን በማኅበረ ቅዱሳን ባለሙያዎች ተሰርቶ ቀድሞ የነበረውን ዲዛይን በድጋሚ ማስተካከያ በማድረግ የወረዳ ማእከሉ ባለሙያዎች በቅርበት እየተከታተሉት ለሁለተኛ ጊዜ በተዋቀረው ሕንፃ አስሪ ኮሚቴ አማካይነት ሊጠናቀቅ ችሏል፡፡

01ww01wy
የገዳሙ መሥራች የሆኑት ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ /መምህር ወልደ ትንሣኤ ግዛው/ የሕይወት ታሪካቸው እንደሚያስረዳው መጋቢት 21 ቀን 1911 ዓ.ም. በቀድሞው በተጉለትና ቡልጋ አውራጃ ኢቲሳ ደብረ ጽላልሽ የተወለዱ ሲሆን፤ በ1921 ዓ.ም. ከግብፃዊው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ዲቁና፤ ነሐሴ 24 ቀን 1933 ዓ.ም. በደብረ ሊባኖስ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም ምንኩስናን፤ በ1940 ዓ.ም. በታዕካ ነገሥት በዓታ ለማርያም ገዳም ከኢትዮጵያዊው ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ ቁምስና፤ ግንቦት 30 ቀን 1979 ዓ.ም. በብፁዕ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ኤጲስ ቆጶስ ሆነው ተሹመዋል፡፡
በአዲስ አበባ በቀጨኔ መድኃኔዓለም፤ በመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም፤ በመናገሻ ቅዱስ ጊዮርጊስ፤ በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ፤ በድሬደዋ ቅዱስ ሚካኤል፤ በሐረርጌ ሀገረ ስብከት ጅጅጋ፤ ኦጋዴን እና አሰበ ተፈሪ ካገለገሉባቸው አድባራትና ገዳማት ውስጥ ይጠቀሳሉ፡፡ በ1946 ዓ.ም. ወደ ቀድሞው ጨቦና ጉራጌ አውራጃ፤ በአሁኑ ደቡብ ምዕራብ ሸዋ ሀገረ ስብከት ወሊሶ /ግዮን/ ከተማ በመምጣት አሁን ገዳሙ በሚገኝበት ቦታ ላይ መሬት በመግዛት አዳራሽ ሠርተው ከእግዚአብሔር በተሰጣቸው ጸጋ በአጋንንትን የተያዙ ሕሙማን እየፈወሱ ቆይተዋል፡፡ አገልግሎታቸው ወደ ቀድሞው ንጉሥ ዐፄ ኃይለ ሥላሴ በመድረሱ የያዙትን ቦታ አስፍተው እንዲያገለግሉ መሬት እንዲሰጣቸው አድርገዋል፡፡

በ1971 ዓ.ም. የሚያገለግሉበት አዳራሽና ሰፊውን ቦታ በደርግ እንደሚነጠቁ የተረዱት ብፁዕነታቸው በሚያገለግሉበት አዳራሽ ጽላት በማስገባት ቤተ ክርስቲያኗ ተመሠረተች፡፡

01www01wwww
ብፁዕ አቡነ ዲዮስቆሮስ ከ10 ሚሊዮን በላይ ከኢትዮጵያ እና ከመላው ዓለም በአጋንንት የተያዙ ሕሙማንን ከእግዚአብሔር በተሰጣቸው ሀብተ ፈውስ እንደፈወሱ መረጃዎች ያመለክታሉ፡፡

ብፁዕነታቸው ጥር 18 ቀን 1989 ዓ.ም. ዐርፈዋል፡፡
ሕንፃ ቤተ ክርስቲያኑ ግንቦት 20 እና 21 ቀን 2007 ዓ.ም. በቅዱስ ፓትርያርኩ ተባርኮ ጽላቱ የሚገባ ሲሆን፤ ዓመታዊ የእመቤታችን የንግስ በዓል በድምቀት እንደሚከበር ኮሚቴው አስታውቋል፡፡
ምእመናን በዚህ ታሪካዊና የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ሲከናወንበት በነበረው ገዳም ተገኝተው የበረከቱ ተሳታፊ እንዲሆኑ የገዳሙ አስተዳደርና ሕንፃ አስሪ ኮሚቴ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡

Monday, June 8, 2015

እሙሀይ ብርሐን - ዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም

በዲማ ቅዱስ ጊዮርጊስ ገዳም 【በቤተክርስታን ቅፅር ግቢ ውስጥ የሚኖሩት 】እሙሀይ ብርሐን እናታችን የተሰጣቸው ፀጋ በጣም ለሰሚው ጆሮ በጣም ሊከብድ ይቻላል እናታች በቤተክርስታን ቅፅር ጊቢ መኖር ከጀመሩ ከ30 ዘመናት በላይ ሆኗቸዋል በነዚህ ዘመናት ባዶ ሜዳ ላይ ተቀምጠው ☞ ዝናብ ሲዘንብ እሳቸው የተቀመጡበት ቦታ ደረቅ ሆኖ እሳቸውንም ሆነ የተቀመጡባትን አካባቢ ዝናብ አያገኘውም እሙሀይ በዚህ ሲኖሩ የሚመገቡት ቱልት የተባለውን ቅጠል ሲሆን እናታችን ብዙ ተማዕራትን በተለያየ ግዜ ሲያደርጉ በአካባበው ምዕመናን ታይተዋል ከዚህ አልፎ በዋልድባ ገዳም የሚኖሩ አባቶች ከሰማይ በቀስተደመና አምሳል ከሰማይ ብርሐን ሲወርድላቸው አይተው መጥተው የእሙሀይን በረከት በረከትዎ ይድረስብን እናታችን ብለው እጅ ነስተዋል የእናታችን በረከት በጣም አስገራሚ እና አስደናቂ ነው እሰኪ ሁላችንም የእሙሀይ ብርሐን በረከት በየአለንበት ይድረሰን እሙሀይንም በቦታው ተገኝተን የበረከቷ ተካፍይ ያድርገን።



Wednesday, June 3, 2015

የቅዱስ ገብርኤል ጽላት በአንድ አባት ራእይ ተገኘ



ታላቅ የምስራች!!
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን በአለልቱ ወረዳ ልዩ ስሙ ቁምጤ በተባለ አካባቢ የአብሳሪው ቅዱስ ገብርኤል ጽላት፣ ልዩ የፀበል ቦታና ሌሎች የብራና መፃሕፍት በአንድ ቅዱስ አባት ራእይ( ህልም) አማካኝነት ተገኝቷልና መጥታችሁ ጎብኙ። አካባቢው ከመዲናችን አ.አ 55 km ወጣ ብሎ የሚገኝ ቅርብ ቦታ ስለሆነ መጥታችሁ የበረከቱ ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ ጥሪያችንን በእግዚአብሔር ስም እናቀርባለን።
እባካችሁ ይህን መልዕክት ለሌሎች በማካፈል ለሁሉ እንዲደርስ የበኩላችንን አስተዋፅኦ እናድርግ


 በአለልቱ አካባቢ ስለተገኝ የቅዱስ ገብርኤል ጽላት አጭር መረጃ (ለማታውቁት)፦ ዕለቱ ስኞ ግንቦት 24 /2007 ዓም የተክልዬ የበአል ቀን ነበር። በነገራችን ላይ አለልቱ ማለት የአባታችን ተክለኃይማኖት የትውልድ ቦታ እና የበርካታ አብያተ ቤተ ክርስትያናትና ገዳማት መገኛ ወረዳ ናት። እናም እኝህ በፎቶው ላይ የምታዩዋቸው ባህታዊ አባት የመጡት ከሌላ አካባቢ ሲሆን በእግዚአብሔር መልካም ፈቃድ በህልም (በራእይ) ተገልፃላቸው ወደዚህ አካባቢ በመምጣት ፅላቱ የተገኘበት ቦታ ላይ ሄደው ቁፋሮ እንዲጀመር ያዛሉ። ሆኖም ግን ያው እንደምናውቀው አንዳንድ የኃይማኖት መሪዎችና መናፍቃንን ጨምሮ ጥቂት ሰዎች " አባ ምን ነካቸው ይቃዣሉ እንዴ " እያሉ በጥርጣሬ ሲያሟቸውና ሲሳለቁባቸው ነበር። ነገር ግን ከጥቂት ሰአታት በኋላ እግዚአብሔር ለሁሉም ያስደመመና ያስደነገጠ ልዩ ተአምራቱን አሳየ። እጅግ ግዙፍ ከሆነ ድንጋይ ሥር በጥንታዊ ቆዳ የተጠቀለለና ልዩ መአዛ ያለው ጽላትና የብራና መፅሐፍ ተገኘ። የፀበል ቦታውንም ጭምር። በዚህ ሰአት ቦታው የመንገድ ዳርቻ (አስፋልት) ስለሆነ መንገደኛ ሁሉ ከመኪናው እየወረደ ሁኔታውን ለማየት ይጎርፍ ጀመር። ከመቅፅበትም ሌላ ጉድ ታዬ።

በአለልቱ ከተማ በአባታችን በአባ ገብረ ሕይወት ራዕይ ከተገኘው የቅዱስ ገብርኤል ፅላት ጋር አብሮ የተገኘው 600 አመታትን ያስቆጠረው የብራና መጽሐፍ ይህ ነው። የመለዓኩ ቅዱስ ገብርኤል በረከት በሁላችን ይደር። ቅዱስ ገብርኤል ይጠብቃችሁ።

ታላቅ ተዓምራት- የፈለገ ሕይወት መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፣ወቅድስት ሃና ወቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን

በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ ፲ የሚገኘው የፈለገ ሕይወት መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ፣ወቅድስት ሃና ወቅዱስ ዑራኤል ቤተክርስቲያን ሰሞኑን ታላቅ ተዓምራትን እያሳየ ነው። ሰዎች ይዘባበታሉ እግዚአብሔር ግን ሥራውን እየሰራ ነው፣ ሰዎች ልብ እንበል "በዚያን ጊዜ ብዙዎች መንገዶቻቸውን ይስታሉ" እንደተባለው ዘወትር በአጠገባችን ከከበበን ጠላት ዲያብሎስ ርቀን የቃሉን ድምጽ ሰምተን ወደ እርሱ ብንጠጋ እንባረካለን። ረደኤተ እግዚአብሔር አይለየን አሜን

ደብረ እያሪኮ ቅዱስ ሚካኤል

ምን ዓይነት ጸሎት በየትኛው ሰዓት ልጸልይ? 

ኢትዮጵያውያንና የያዕቆብ የመጨረሻ ልጅ የቢኒዖን (ብንያም)ነገድ

የፈለገ ሕይወት መጥምቁ ዮሐንስ ወቅድስት ሃና ወቅዱስ ዑራኤል ገቢረ ተዓምራት -save waldiba


 

Tuesday, June 2, 2015

ድንቅ ታምር ጃማ ማርያም

ዳግማዊት ጎለጎታ ድንጋይ ገጠም ጃማ ማርያም ቤተ ክርስቲያኗ የተመሰረተችው በ17ተኛው ክ/ዘ በልጅ እያሱ ዘመነ መንግስት እንደተሰራች የሚነገርላት ጃማ ማርያም ዳግማዊት ጎለጎታ እንድትባል ያስቻላት ከዕየሩሳለም ጎለጎታ ቀጥላ ሁለተኛዋ በመሆኗ እና ድንቅና ታምራዊዋ ጸበል ከፈለቀበት ከ1965 ዓ/ም ጀምሮ ደንቅ ታምር እየሰራ የገኛል ለምሳሌ :-\አይነ ስውራንን ፥መንፈስ የተጠናወታቸውን ፥አካላቸው ሽባ የሆነውን ፥አፋቸው የማይናገረውን፥የዘመኑ በሽታ(HIv)ን ጨምሮ እና ሌሎችንም በርካታ በሽታወችን የምፈውሰው ከድንጋይንና ከተራራ ላይ የሚፈልቀው ጸበል ድንቅ ታምር እየሰራ ስለመሆኑ ታምሩ ይመሰክራል በመሆኑም ግንቦት 21/2007ዓ/ም የንግስናዋ እለት ከ2000 በላይ ምዕመናን ለበዓሏ ታድሟል ውድ ጓደኞቸ ሼርና ላይክ በማድረግ ከዚህ ታምር ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ በእግዚዓብሄር ስም አሳሰብኋችሁ የእግዚዓብሄር እና የቅድስት ድንግል ማርያም በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን፡፡







Monday, June 1, 2015

ፓሊካርፕ (ከ69-155ዓ/ም) የተጋድሎ ሜዳው ምስክር


ትርጉም ዘላለም ቸርነት
ጌታ ኢየሱስ እንዲህ አለ፡- ‹‹ቤተክርስቲያኔን በዚህች ዐለት ላይ እሠራለሁ፤የገሃነም ልጆችም አይቋቋሟትም›› ማቴ. 16÷18
እናም በአስገራሚ ክብርና ኃይል ቤተክርስቲያኑን መሠረተ፡፡ ክርስቶስ ከመቃቭር ተነሣ ሞተ ይይዘው ዘንድ አልቻለምና፡፡ ሕያውነቱንም በግልጥ አሳየ፤ በሃምሳኛውም ቀን መንፈሱን በእሳት ልሳን መልክ ላከው፡፡ ይህም ፈሪዎችና ግራ የገባቸውን ደቀ መዛሙርት ቆራጥና ጀግና የመስቀል አርበኞች አደርጋቸው፡፡ እነርሱም በሽተኞች ፈውሱ ሙታንን አስነሱ፤ በግልጥነትም ወንጌልን ስበኩ በአገልግሎታቸውም በሺህ የሚቆጠሩ ሰዎች ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ፈለሱ፡፡ የአይሁድ ሃይማኖት መሪዎች ደቀመዛሙርትን ገርፈው ዳግመኛ ስለ ክርስቶስ እንዳይናገሩ ቢያስጠነቅቋቸውም ምላሻቸው ግን ‹‹ከሰው ይልቅ ለእግዚአብሔር ልንታዘዝ ይገባናል፤ ያየነውንና የሰማነውን ከመናገር ዝም አንልም የሚል ሆነ፡፡


መከተል የሞት ፍርድ የሚያስከትል ወንጀል ሆኖ እንዲቆጠር አዋጅን አወጡ፡፡ በአገሪቱ በሚከሰተውም አደጋና ጥፋት
ክርስቲያኖችን ተጠያቂ ማድረግ ጀመሩ፡፡ አንድ የጥንት ክርስቲያንእንደተናገረው የጎርፍ መጥለቅለቅ ከመጣ ድርቅና ርሃብ ከሆነ ወይም መቅሰፍት ከወረደ እነዚህ አረማውያን እንዲህ ሲሉ ይጮሃሉ ‹‹ክርስቲያኖቹን ለአንበሳ እንወርውራቸው!›› በዚህ ዘመን በክርስቲያኖች የማምለኪያ ቤቶች ውስጥ ዓይነት የአማልክት ምሥል ስለሌለ አረማውያን ክርስቲያኖችን በአማልክት ሕውና እንደማያምኑ ተረድተዋል፡፡ ስለዚህም ክርስቲያኖችን የሚተሯቸው ‹‹አምላክ የለሾች›› ብለው ነበርለለ ነገሩ ገን የተገላቢጦሽ ነበር 2ኛ ዮሐ.9 በየሐንስ ራእይ ላይም በስደቱ ዘመን ለነበረችው የሰምርኔስ ቤተክርስቲያን (ፖሊካርፕ የነበረባት) ጌታችን በዮሐንስ
አማካኝነት በላከው ምልእክት በውሸተኞች የሚደርስባቸውን ስድብ እንደሚያውቅላቸው ተናግሯል፤ ራእ 2÷9 ሮማውያን ብዙዎችን የመጀመሪያ የጌታ ደቀመዛሙርት ለሞት አሳልፈው ሰጥተዋቸዋል፡፡ የጳውሎስን አንገት ሲቆርጡ ጰየጥሮስን ሰቅለውታል፡፡ ለሌቹንም በእሳት አቃጥሏቸው፤ በሰይፍ ገደሏቸው ለአውሬ ጣሏቸው፡፡‹‹ዓለም እናንተን ቢጠላችሁ በቅድሚያ እኔን እንደጠላ አስተውሉ እኔን አሳደው ከሆነ እናንተንም ያሳድዷችኋል›› የሚለው የእየሱስ ቃል በጆሮዋቸው እየደወለ ነፍሳቸውን ሰጡ፡፡

የክርስቲያኖች በቁጥር ማደግ ብሎም ለጣዖቶቻቸው አንሰግድም ማለታቸው የሮም ገዢዎችን በፍርሃት ላይ ስለጣላቸው ክርስቶስን የጥንት ቤተክርስቲያን ታሪክ እደሚነግረን የጌታ ሰማዕታት ሕይወታቸውን በወንጌል ምክንያት ለሞት አሳልፈው ሲሰጡ በድንጋጤና በመርበትበት ሳይሆን ፊታቸው ከተስፋቸው በተገኘ ብርሃን ፈክቶና ጉዳዮቻቸው አማውያንን ግራ በሚያጋባ የደስታ ዝማሬ ታጅበው ነበር፡፡ እንዲህ እየዘመሩ ነበር የሚሞቱት ‹‹ለወደደን ከኃጢያታችንም በደሙ ላጠበም ለአባቱም መንግሥት ካህናት እንደንንሆን ላደረገን ለእርሱ ክብር ይሁን!›› በዚያ በከፋ የስደት ወቅት ቤተክርስቲያን በሮም ግዛት ውስጥ እያደገች እየጠነከረች እየበዛችና እየሰፋች ሄደች፡፡ ከዚህም በኋላ በሐዋርያትና በደቀመዛሙርት እግር የሚተካ አዲስ ትውልድ ብቅ አለ፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ፖሊካርፕ ግንባር ቀደም ተጠቃሽ ነው፡፡ ፓሊካርፕ በወጣትነቱ በሐዋርያው ዮሐንስ እግር ሥር ሆኖ
የተማረ ነበር፡፡ ብዙ ሰዎችንም ወደ ዘላለም ሕይወት መርቷል፡፡

የሰምርኔሱ ጳጳስ ፖሊካርፕ በእምነቱ ምክንያት በርካታ የመከራና የእስር ዓመታትን አሳልፏል፡፡በከሎስየም የትርኢት ሜዳ(Arena) መሃል አንድ ወጣት ቆሟል፤ አንድ አንበሳም በወጣቱ ዙሪያ ይንጎራደዳል፡፡ የተሰበሰበው ሕዝብ ምንም ዓይነት ድምጽ ሳያሰማ የሚሆነውን ይከታተላል፡፡ ከንጉሳዊ ዙፋን በፈገግታ ይመለከተዋል፡፡ በዚህ በሰርምኔስ ግዛት ማንኛውም ክርስቲያን እምነቱን ካልካደ ይህ ወጣት በዚህ የትርኢት ሜዳ አንበሳ ፊት የቆመው፤ ‹‹ወደዚህ ና›› አለ ገዢው በወጣቱ ላይ እየጮኸ

‹‹አንተ ወጣት ነህ፤ ገናም ረጅም የሕይወት ዘመን ይጠብቅሃል አሁንም አልዘገየህም አንዳንዶቹ ጓደኞችህ በቄሳር ምለዋል፡፡
አንተም በቄሳር ብትምል አንበሶቹን አርቅልሃለሁ እናም በቄሳር ማልና በሕይወት ኑር›› አለውው፡ ወጣቱ ግን ራሱን በአሉታ በመነቅነቅ ወደ አንበሳው ተጠጋ፡፡ አንበሳው ቀጥ ብሎ ከቆመ በኋላ ወደ ወጣቱ ተስፈንጥሮ ዘለለ፡፡ ለቅትበት ከታገሉ በኋላ አንበሳው ወጣቱን በጠንካራ ጥርሶቹ ዘነጠለው፡፡ የተሰበሰበውም ሕዝብ በደስታ እያጨበጨበ ‹‹ሞተ ለአማልክት የለሾች ሲል ጮኸ፡፡ ከገዢዎቹ አንዱ እንዲህ አለ ‹‹ይሄ ወጣት ተራ አማኝ ነበር፡- ሌላውም ቀጠለና ‹‹ፓሊካርፕን እንፈልጋለን መሪያቸውን፡፤ ሞተ ለአማክት የለሾች! ሞት ለፖሊካርፕ!›› ሲል በትርኢት ሜዳው የተሰበሰበው ሕዝብ ሁሉ በአንድ ድምጽ‹‹ሞተ ለአማልክት የለሾች !ሞት ለፖሊካርፕ! ሲል በትርኢት ሜዳው የተሰበሰበው ሕዝብ ሁሉ ሁሉ በአንድ ድምጽ ‹‹ሞተ ለአማልክት የለሾች! ሞተ ለፖሊካርፕ!›. አለ መጮሕ ጀመረ፡፡ በዚህ ጊዜ ፖሊካርፕ በወታደሮች ተይዞ እንዲመጣ ትእዛዝ ተሰጠ፡፡ ወታደሮችተይዞ እንዲመጣ ትእዛዝ ተሰጠ፡፡ ወታደሮቹ ፖሊካርፕን ባገኙት ጊዜ በትርኢቱ ሜዳ ወደ ተሰበሰበው ሕዝብና ወደ ሮማው ገዢ ለመውሰድ አጣደፉት፡፡ በወታደሮች ታጅቦ የክርስቲያኖች መሪ የተባለው ፖሊካርፕ እንደመጣ ደም የጠጠማው አረማዊ ሁሉ በአነድ ድምጽ ‹‹ሞተ ለፖሊካርፕ!›› ሲሉ ጮኹ፡፡ የወይን ጠጅ ቀለም ያለው መቀነት ታጥቆ ወርቃማ ልብስ የለበሰው የሮማው ገዢ ከዙፋኑ ተነስቶ በሰገነቱ ለይ ቆመ፡፡ በአቧራ የቆሸሸውን ፖሊካርፕን በትክታ ፈገግ ብሎ ተመለከተው፡፤ እጁንም አወዛውዞ የሕዝቡን ጩኸት ዝም አወሰኘና፤

‹‹አንተ የክርስቲያኖች አስተማሪ ፖሊካርፕ ነህ?››
‹‹አዎን እኔ ነኝ›› መለሰ ፖሊካርፕ፡፡
‹‹በዚህ በሽምግልና ክብርህን የምትጠብቅ ይመስለኛል›› ቀጠለ ገዢው፡-‹‹በቄሳር ስም ማልና ራስህን አድን በተጨማሪም ወደ እነዚህ እስረኛ ክርስቲያኖች ፊትህን መልስና ጣትህን በመጠቆም፡- እናንተ አምላክ የለሾች ጥፉ! ብለህ አውጅ›› አለው፡፡ፖሊካርፕ ግን በተቃራኒው ፊቱን ወደ ትርኢቱ ተመልካች ሕዝብ አድርጎ ጣቱንም በእርሱ ላይ በመቀሰር ‹፣እናንተ አምላክ የለሾች ራቁ›› ሲል ዓይኖቹን ወደ ሰማይ አንሥቶ ጮኸ፡፡ በዚህ ጊዜ ሕዝቡ ጥርሱን አፋጨበት፡፡ ‹‹ዕንዴት ቢደፈፍርን ነው አምላክ የለሾች የሚለን?›› ሲሉም ብንዴት ተንቀጠቀጡ፡፡ ገዢው ግን አሁንም ፖሊካርጵን ሊያጠምደው ፈለገና ‹‹በቄሳር ማል በሰላም እለቅሃለሁ፤ እናም ክርስቶስ ካደ›. አለው፡፡ ፓሊካርፕ ግን ቀጥ- ብሎ እንደቆመ፡- ‹‹ለ86 ዓመታት ያህል የእርሱ አገልጋይ ነበርሁ፤ በእነዚህም ዓመታት አንድም ቀን አስከፍቶኝ አያውቅም፤ ታዲያ ያዳነኝን ንጉሤን መካድና መስደብ እንዴት ይሆንልኛል?›› ሲል ተናገረ፡፡
‹‹በቄሳር ማል፤ ገዢው በንዴት ጦፎ ጮኸ
‹‹በቄሳር እንድምል እንዲያው በከንቱ አትልፋ በግልጽ
እንድትሰማኝ እፈልጋለሁ እን ክርስቲያን ነኝ››
‹‹ አዚህ አደገኛ አውሬዎች አሉ›› ገዢው ማስፈራራቱን ቀጠለ
‹‹ሃሳብህን የማትለውጥ ከሆነ ለእርሱ ወርሬ እሰጥሃለሁ››
‹‹አምጣቸው!›› ፓሊካርፕ በጽናት መለሰ፡፡
‹‹አውሬዎቹን የማትፈራ ከሆነ በሕይወት ሳለህ በእሳት
አቃጥልሃለሁ›.
‹‹ጥቂት ጊዜ ነድዶ በሚጠፋ እሳት ልታስፈራራኝ አትሞክር›› አለ
ፖሊካርፕ ነገር ግን እግዚአብሔርን ለማያውቁ የተዘጋቸውን
ዘላለማዊ ገሃነመ እሳት ዘንግተሃል ለምን ትዘገያለህ? ፊትህ ናና የወደድኸውን አድረርግ›› ከሕዝቡ መሃል አንድ ሰው እንዲህ ሲል በድንግት ጮኸ ‹‹ይሄ የክርስቲያኖች አባት የሚባለው ነው ፤ ብዙዎችንም ለአማልክቶቻችን እንዳይሰግዱ ያስተማረ ነው፤ አቃጥሉት ወታደሮቹ በዚህ ጊዜ ፖሊካርፕን ከምሰሶ ጋር ሊያስሩት መጡ፡፡ፖሊካርፕም ‹‹በእሳቱ ነበልባል ፊት እንድጸና የሚያጠነክረኝ እርሱ በመንደጃው ምሶሶ ላይ ሳልታሰር ጸንቼ እንድቆም ያበረታኛል.›› አለ፡፡ ከሥሩም እንጨትና ጭራሮ ሰብስበው ዘይት በማፍሰስ እሳት ለኮሱበት፡፡ በእሳቱ ነበልባል ውስጥ የጶሊካርፕ ጸሎት ከፍ ባለ ድምጽ ይሰማል፤ እንዲህ ሲል፡- ታላቅ አምላክ እግዚአብሔር ሆይ አንተ የተወደደው ልጅህ የኢየሱስ ክርስቶስ አባት ነህና በእርሱም አንተን እናውቅህ ዘንድ ተሰጥቶናልና ተመስገን፡፡ ስለዚህች ቀንና ሰዓት እባርክሃለሁ ምክኒያቱም ከሰማዕታት አንደ አንዱ ሰለተቆጠርሁኝ አንተ እውነተኛ እና ታማኝ አምላክ ነህ፡፡ ላንተ ከአሁን እስከ ዘላለም ድረስ ክብር ይሁንልህ አሜን!›. የእሳቱ ወላፈን እና ብርታት ወደ ላይ እየተንቀለቀለ ይታያል፤ ነገር ግን በዚያው ቅጽበት ፖሊካርፕ በሞት ፊት የነበረው ድፍረትና ጥንካሬ በስደት ላይ ለነበሩት ክርስቲያኖች ክርስቶስን በታመን እንዲኖሩና እንዲጸኑ ተጨማሪ ብርታትን ይሰጣቸው ነበር፡፡
ቤሪያ ጋዜጣ
ቁጥር 1 1996