Wednesday, August 30, 2017

የሰማዕቱ ቅዱስ መርቆሬዎስ ድንቅ ተአምር

በደቡብ አፍሪካ ደርባን ያደረገው
ጥ ብልው ቁጭ እንዳሉ ቡኒ የፓሊስ ልብስ የለበሰ ቀይ ወጣት እናቴ አትፍሪ ምን ሆነሽ ነው አትፍሪ ፓሊስ ነኝ ይላቸዋል ወዲያው አንድ እብድ ድንጋይ ወርውሮ የሱፐር ማርኬቱን መስታወት ይሰብራል ያ ድንጋይ ናድያ ቀሚስ ላይ ቁጭ ይላል ወደውስጥም ዘልቆ አትፍሪ አዕምሮውን የሳተ ሰው ነው ብሎ ያረጋጋቸዋል ዘጠኙ የስራ ባልደረቦቻቸው ሲመጡ በሆነው ነገር ይደነቃሉ ፓሊስም ስላዮ ደስታቸው እጽፍ ሆነ ሆቴላቸው በር ደርሰው አስፓልት ሊሻገሩ ሲሉ ናዲያ ብሎ በስማቸው ጠርቶ ይጨብጣቸውና የት ይግባ የት አያስተውሉም ዘጠኙ ሰዎች የራሳቸውን ጨዋታ ይዘዋልና አላስተዋሉም ያው ነጭ ፓሊስ አግኝታ ወሬ ይዛለች ብለው ትተዋቸዋል ሆቴሉ በር ላይ ላሉት ሴኩሪቲዎች ሲነግሩዋቸው ቡኒ ልብስ እኛ ሐገር የሚለብስ ወታደር የለም ጉዳዮን ለደህንነት ክፍሉ ያመለክታሉ እንዲህ አይነት ሰው አናውቅም ይህ ኢኒፎርምም የለንም ስለተፈጠረው የጥበቃ ክፍተት ይቅርታ ይጠይቃሉ መጀመሪያ አልፈዋቸው የሄዱት ወንበዴዎች 5 ሰው እዛው መንገድ ገድለዋል በዛው ቅጽበት ከዘጠኙ 8 ኢ አማኒ ናቸውና አልተገረሙም መኝታ ክላቸው ገብተው እጃቸውን ሲያዮት በቅባ ቅዱስ እርሶዋል ለካ ናዲያ ብሎ በስሜ የጠራኝ በእግሊዘኛ ሳይሆን በአረብኛ ነበር ያወራኝ ታዳጊው ሰማዕት ነው ይህ እንዴት ይሆናል ብለው ያነባሉ ምስጋናም ያቀርባሉ እዛው ደቡብ አፍሪካ በተመሳሳይ በሌላ አመት ቅዱስ መርቆሬዎስ በገሐድ በመገለጥ ከአደጋ ታድጎዋቸዋል ይህ ታምር ሲሰራ ወላጅ እናቴም ነበረች ይህች ሴት ይህን ነጭ የት አውቃ ነው የሲአይ ኤ ሰላይ ሳትሆን አትቀርም እዛ ኮንፍረንስ ሞል ስንፈራ ስንቸር ለምን አልጠራችውም አሁን ከየት መጣ ደግሞ ሱፐር ማርኬቱ ውስጥ ሳየው አይኑ እሳት ይመስላል ኩዋሱ አይታይም እያልኩኝ አምቻለው ብላኛለች በወቅቱ ስለ እምነት ብዙ ዕውቀቱ ባይኖረኝም የሴኩሪቲዎቹ አናውቀውም ማለትና ሳይሰናበትን መሄድ ገርሞኛል ብላለች ይህ ምስክርነት በአሮጌው ካይሮ በሚገኘው የሰማዕቱ አቡ ሰይፌን ገዳም በተአምራቱ መዝገብ ላይ አጽፈውታል ድንቅ አድራጊው ሰማዕት ከነፍስና ስጋ አጥማጅ ክፉ መናፍስት ምልጃው ይታደገን አሜን ለአምላከ መርቆርዬስ ክብር ይግባው እልልልልልልልልልልልልልልልልልል

በወረብ አብሮ የሚሳተፈው የቅዱስ መርቆርዮስ ስዕል

Sunday, August 27, 2017

122 አመት የሆነው ታቦተ አቡነ አረጋዊ በተኣምር ተገኘ

ሰላም እንደምን አላችሁ፡ 21/12/2009ዓ.ም በ ሎዛ ማርያም ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን(ብርጭቆ ማርያም) ለአገልግሎት ነው የሄድኩት ቅዳሴ ካለቀ በኀላ ተአምረ ማርያም ተነቦ በአውደ ምህረት አንድ አባት ፦ ነሀሴ 7ቀን በቤተልሔሙ ጋር ብርሀን አይቻለው አንድ ነገር ይኖራል ስለዚህ ቆፍረን ማየት አለብን ብለው ለ አለቃው ይነግሯቸዋል እሳቸውም እሺ በማለት ከ አባቶች, ዲያቆናትና ምእመን ባለበት ሲቆፈር የ ብረት ሳጥን በ ፎቶ እንደምታዩት ብዙ መስቀል ፡ ጽና፡ ማዕጠንት፡ እናም ታቦተ አቡነ አረጋዊ እና ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ሆኖ በ አልባስ ሆኖ ተገኘ፡፡ ሳጥኑ ላይ በ1878 ዓ.ም ተብሎ ተጽፎበታል ማለትም ወደ 122 አመት የሆነው ነው፡ እግዚአብሄር ይመስገን በ ህይወቴ ለመጀመሪያ ግዜ እንዲህ ሲገጥመኝ፡፡ ተመስገን ተመስገን ተመስገን
በረከታቸው ይደርብን አሜን፡፡