Showing posts with label ታቦተ አቡነ አረጋዊ. Show all posts
Showing posts with label ታቦተ አቡነ አረጋዊ. Show all posts

Sunday, August 27, 2017

122 አመት የሆነው ታቦተ አቡነ አረጋዊ በተኣምር ተገኘ

ሰላም እንደምን አላችሁ፡ 21/12/2009ዓ.ም በ ሎዛ ማርያም ቅድስት ድንግል ማርያም ቤተክርስቲያን(ብርጭቆ ማርያም) ለአገልግሎት ነው የሄድኩት ቅዳሴ ካለቀ በኀላ ተአምረ ማርያም ተነቦ በአውደ ምህረት አንድ አባት ፦ ነሀሴ 7ቀን በቤተልሔሙ ጋር ብርሀን አይቻለው አንድ ነገር ይኖራል ስለዚህ ቆፍረን ማየት አለብን ብለው ለ አለቃው ይነግሯቸዋል እሳቸውም እሺ በማለት ከ አባቶች, ዲያቆናትና ምእመን ባለበት ሲቆፈር የ ብረት ሳጥን በ ፎቶ እንደምታዩት ብዙ መስቀል ፡ ጽና፡ ማዕጠንት፡ እናም ታቦተ አቡነ አረጋዊ እና ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ሆኖ በ አልባስ ሆኖ ተገኘ፡፡ ሳጥኑ ላይ በ1878 ዓ.ም ተብሎ ተጽፎበታል ማለትም ወደ 122 አመት የሆነው ነው፡ እግዚአብሄር ይመስገን በ ህይወቴ ለመጀመሪያ ግዜ እንዲህ ሲገጥመኝ፡፡ ተመስገን ተመስገን ተመስገን
በረከታቸው ይደርብን አሜን፡፡