Showing posts with label ከፕሮቴስታንት ወደ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ. Show all posts
Showing posts with label ከፕሮቴስታንት ወደ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ. Show all posts

Tuesday, August 11, 2015

ጉዞ ከፕሮቴስታንት ወደ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ (ምስክርነት)

እህታችን የፕሮቴስታንትን ድርጅት ሃይማኖቷ እንዲሆን እና ድርጅቱን እንድትከተል የሆነበት ምክንያቱ እንዲህ ነው….. በእንጀራ አባቷ ጓደኛ ምክንያት በመታለል ሲሆን የኦርቶዶክስ ሃይማኖቷን እንድትክድ እና ወደ ፕሮቴስታንት ድርጅት እንድትቀላቀል፤ የፈለገችውን ገንዘብ ያህል እንደሚሰጧት፤ ልብስ፤ ጫማ፤ ትምህርቷን በሰፊው እየከፈሉ ሊያስተምሯት ቃል ገብተው ነበር። እንደወሰዷትም የኑፋቄን ትምህርት ለሦስት አመታት በተከታታይ አስተማሯት፤ ገንዘብም ሰጧት፤ ማህተቧን ከአንገቷ በጥሳ እንድትጥል እና እንድትረግጥ አደረጉ….መላእክትን እንዳትፈራ እንደተራ ነገር እንድትቆጥር አደረጉ፤ ቅዱሳንን ማቃለል ሥራየ ብላ እንድትይዝ አደረጉ፤ እመቤታችንን መዝለፍን አስተማሯት……እንደ ልጅቱ አገላለጽ ወይም በአንደበቷ እንደመሰከረችው ፓስተር ተብየዎች የፕሮቴስታንትን ድርጅት የሚከተሉ ወጣቶች እና እሷን ጭምር ትዳር ከመያዛችሁ በፊት ሴክስ አርት ስለሆነ ኑና እናስተምራችሁ አያሉ ያስቸግሯቸው እንደነበር እና ሌሎችም የተደበቁ የተሐድሶ አጀንዳዎችን በይፋ ነገረችን ….ያሳዝናል። ከእኛ ወገን መስለው ያሉ ነገር ግን ልባቸው መናፍቅ የሆኑ ስንቶችን ዘረዘረቻቸው……..ብቻ የአቡነ ተክለሃይማኖት አምላክ ይጠብቀን…..አጽራረ ቤተክርስቲያንን ያስታግስልን አሜን። መረጃዎችን ለወደፊቱ ለሚከተለው ክፍል እንደምትሰጥ ቃል ገብታለች። እኛም ለመስማትም ለማየትም እንፈልጋለን እንጠብቃለን። የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ቤተክርስቲያናችንን ይጠብቅልን አሜን።
እግዚአብሔር ፈቅዶ ከዚህች የፕሮቴስታንት እምነት ተከታይ የነበረች እህት ጋር ለተወሰነ ቀናት ተነጋግሬ፤ ስህተቷን አምና ወደ ቀደመችው እና ትክክለኛ ሃይማኖቷ እንድትመለስ ምክንያት ብሆንም ይህን ላደረገ የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ክብር ምስጋና ይገባዋል። ምስክርነቷን ከተጠመቀች በኋላ ነሐሴ 3 ቀን 2007 ዓ.ም ጎንደር አደባባይ አቡነ ተክለሃይማኖት ቤተክርስቲያን ሰጥታለች።

ተአምር በ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ቤተ ከርስቲያን /ሽሬ/