Showing posts with label ጃማ ማርያም. Show all posts
Showing posts with label ጃማ ማርያም. Show all posts

Tuesday, June 2, 2015

ድንቅ ታምር ጃማ ማርያም

ዳግማዊት ጎለጎታ ድንጋይ ገጠም ጃማ ማርያም ቤተ ክርስቲያኗ የተመሰረተችው በ17ተኛው ክ/ዘ በልጅ እያሱ ዘመነ መንግስት እንደተሰራች የሚነገርላት ጃማ ማርያም ዳግማዊት ጎለጎታ እንድትባል ያስቻላት ከዕየሩሳለም ጎለጎታ ቀጥላ ሁለተኛዋ በመሆኗ እና ድንቅና ታምራዊዋ ጸበል ከፈለቀበት ከ1965 ዓ/ም ጀምሮ ደንቅ ታምር እየሰራ የገኛል ለምሳሌ :-\አይነ ስውራንን ፥መንፈስ የተጠናወታቸውን ፥አካላቸው ሽባ የሆነውን ፥አፋቸው የማይናገረውን፥የዘመኑ በሽታ(HIv)ን ጨምሮ እና ሌሎችንም በርካታ በሽታወችን የምፈውሰው ከድንጋይንና ከተራራ ላይ የሚፈልቀው ጸበል ድንቅ ታምር እየሰራ ስለመሆኑ ታምሩ ይመሰክራል በመሆኑም ግንቦት 21/2007ዓ/ም የንግስናዋ እለት ከ2000 በላይ ምዕመናን ለበዓሏ ታድሟል ውድ ጓደኞቸ ሼርና ላይክ በማድረግ ከዚህ ታምር ተካፋይ ትሆኑ ዘንድ በእግዚዓብሄር ስም አሳሰብኋችሁ የእግዚዓብሄር እና የቅድስት ድንግል ማርያም በረከት ከሁላችን ጋር ይሁን አሜን፡፡