Showing posts with label ፀበሉ ፈዋሽ ዘብር ቅድስ ገብርኤል. Show all posts
Showing posts with label ፀበሉ ፈዋሽ ዘብር ቅድስ ገብርኤል. Show all posts

Sunday, November 22, 2015

ፀበሉ ፈዋሽ ዘብር ቅድስ ገብርኤል


በሰሜን ሸዋ ሀገር በመንዝ ላሎ ምድር (ዘብር ደብረ ምህረት ቅድስ ገብርኤል) አጭር ታሪክ ተአምረኛው ዘብር ቅድስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን የተመሰረተው በ4ተኛው መቶ ክፍለ ዘመን በውል ባይታወቅም ከቀድሞ አባቶች ሲነገር እንደቆየና እንደሚነገረው በንግስት አድሃና ዘመነ መንግስት ነው ተብሎ ይገመታል።ምክንያቱም የኦሪት ሊቀ ካህናት የእንበረም ልጅ የሕዝበ ባርክ የልጅ ልጅ አጽቀ ሌዊ በንግስት አድሐና ዘመነ መንግስት መንዝን አጥምቆ አብያተ ክርስትያናትን እንዳቀና ታሪክ ያስረዳል።

በቀደምትነት ከቀኑት፣ከተመሰረቱት እጅግ ጥቂት አብያተ ክርስቲያናት መካከል አንድ ተአምረኛው ና ፀበሉ ፈዋሽ ዘብር ቅድስ ገብርኤል አንድ ነው። ደብረ ምህረት ተብሎ ስያሜ የወጣለት ይህ ቤተክርስቲያን በአሁኑ ሰአት ለ60አመት ያስተዳደሩት ሊቀ ሊቃውንት አባ አክሊሉ ከ100 አመት በላይ የሆናቸው የዕድሜ ባለፀጋ መንፈሳዊ አባት ሲሆኑ በመንዝና በሰሜን ሸዋ የአብነት ት/ቤት እንዲስፋፋ ያደረጉ ከ50,000 ሽይ በላይ የሚቆጠሩ የቤተ ክርስቲያን ጳጳሳት፣አስተዳዳሪዎች፣ካህናት፣ዲያቆናት፣መዘምራኖች ሊቃውንቶች በአቋቋም በቅኔ በድጓ ያፈሩ ለጵጵስና ተመርጠው ፣የተወለድበትን ሀገር በንጽህና በቅድስና በእውነት በማገልገል የቦታውን ቃል ኪዳን ለመጪው ትውልድ እንዲተላለፍ ያደረጉ የቤተክርስቲያን አባት በአሁኑ ወቅት አሉ። ፎቷቸው ከታች ይገኛል፣ የቦታው ቃልኪዳን የመላአኩ ቅድስ ገብርኤል ታሪኩም ሆነ ቃልኪዳኑ በድርሳኑ በተአምሩ እንዲሁም በመጽሐፍ ቅድስ ላይ ያለው እንዳለ ሆኖ ዳን•3÷24—30 ዳን•8÷15—18 ሉቃስ 1÷8—20 ለቦታው የተሰጠው ክብርና ቃልኪዳን አንድ ባህታዊ አባት መጥተው ከእየሩስሌም ብዙ ቅድሳን መላዕክትም ሳይቀሩ በቦታው ላይ በአፀዱ ላይ እንደ ንብ ስፍርውበታል ብለው ተናግረዋል፣ከዚህም በተጨማሪ በእግዚአብሔር ዘንድ የተወደደና የከበረ የቅድሳን አበው መናህሪያ ማረፊያ የቃልኪዳን ቦታ በመሆኑ የበዓለ ወልድና የአብነ ሃብተማርያም ገዳም ውስጥ የቅድሳን አበው አጽማቸው በመገኘቱ ነው ታሪኩ እንዲህ ነው ። አባ አክሊሉ ተማሪ ሞቶባቸው መቃብር ሲቆፍሩ አፈሩ አልቆ አንድ ወጥ ድንጋይ

 አግኘተው ሲያነሱት አንድ አባት መልካቸው የሚያምር፣ስጋቸው ያልፈረሰ ፣ፂማቸው የሚያምር መስቀላቸው ይዘው ያልቆሸሸ ንጽህ ከነመግነዛቸው ምንም አፈር ሳይነካቸው በመገኘቱ ሲሆን መቃብራቸውም ተመልሶ ተግጥሟል፣ከዚህም ሌላው የሴት መሎክሴ አጽምም ምንም ሳይሆን ተገኝቷል።12ነገ 13÷20—21 በዚህ ቦታ የሚነኘው ድህነት ይህ ተብሎ አይወሰንም በተለይ አባቶች (መስቀል፣መቋሚያ)ይዘው ፀሉት ሲያደርሱ ችግር የደረሰበት ምዕመኑ (መገበሪያ—ይዞ የተቻለውን ያህል ስንዴ፣ጧፍ፣ጣኑን፣ዘቢብን)ይዞ ቀርቦ የደብሩ ካህናት ጸሎት አድርገው ኃይል አጋንንትን ይጣልላችሁ ብለው (መስቀልና መቋሚያ ዘቅዝቀው ፀሎት ያደርጋሉ ንስሀ ገብቶ ፀሎት የተደረገለት ሁሉ ድህነት ያገኛል)። መተቱም፣አጋንቱም ይታሰራል ፣የተበደለውም ፣የተቀማውም፣የተዘረፈው፣በተለያየ አጋንት ተይዞ ሃብት ንብረቱ አእምሮው እውቀቱ የተበተነበት፣ትዳር ሰላም የሌለው፣ ከቤተሰብ ጋር የሚጋጭ፣ስራ ወይም ትዳር እንቢ ያለው የተለያየ ችግር ያለበት በቅዱስ ገብርኤል ቃልኪዳን ድህነትን ያገኛል።

የቅዱስ ገብርኤል ጽላት በአንድ አባት ራእይ ተገኘ